Untitled 1 Untitled 1
International  Distribution Centers
Click Here to find Distributors









Join our mailing list!
enter your email

(Your shopping cart is empty)




Main Line (800)672-6380

State/city

Phone NO

State/city

Phone NO

Ottawa

613-400-1599

Dallas

214-727-7939

Calgary

403-478-8498

Houston

214-727-7939

Vancouver

604-318-0915

Denver

720-212-3592

Seattle

206-769-5446

DC

571-239-7001

Las Vegas

702-719-9258

OH

614-989-1007

Boston

857-247-2002

MN

952-393-4700



የቃሊቲው መንግስት

በሲሳይ አጌና

 

ሲሳይ አጌና ነፃው ፕሬስ ሲወለድ የነበረ፣ እስከ ምርጫ 97ም  የቀጠለ ጋዜጠኛ ነው፤ታስሮ ፈቃድ እስኪከለከል ነጻው ፕሬስ ውስጥ ኢትኦጵ ጋዜጣና መጽሄትን ሲያዘጋጅ ቆይቷል፤ነፃው ፕሬስ ከፍተኛ እመርታ ባሳየበት እና ከፍተኛ  አደጋ በደረሰበት በምርጫ 97ም በከፍተኛ ደረጃ የተሳተፈና ከፍተኛውን ዱላ የተቀበለ ጋዜጠኛ ነው፤ በአለፉት ሃያ አመታት ፕሬሱ ከአቶ መለስ መንግስት ጋር የሞት ሽረት ትግል ሲያደርግ ሲሳይ አጌና ከግንባር ቀደሞቹ ውስጥ አንዱ ነው:: ለዚህም ውለታው የአቶ መለስን የተለያዩ እስርቤቶችን በተደጋጋሚ ጎብኝቷል እንዲያውም የማዕከላዊ እስርቤት ቋሚ ደምበኛ ከሚባሉት ውስጥ ሲሳይ ቀዳሚ ነውሲሳይ በዚህ መፅሃፉ የቃሊቲውን እስር ቤትና የፍትህ ስርዓቱን ያስጎበኘናል:: አቀራረቡ እንደ ስርዓቱ ሰለባ ሆኖ ሳይሆን እንደ አንድ ነፃ ጋዜጠኛ ዳር ሆኖ ፍርዱን ለአንባቢ በመተው ነው ከብዕሩ በላይ ያስገረመኝ የበደል ስሜቱን ተቆጣጥሮ ያልተዛባ ታሪክ ለትውልድ ለማስተላለፍ መጣሩ ነው ይተኩሷል እንደ ገብርዬ ነበር ያለው ቴዎድሮስ? ታገሷል እንደ ሲሳይ ልበል እኔም ::

አክቲቪስት እና አርቲስት  ታማኝ በየነ

    አገርና ወገን ላይ የሚሠራው ግፍ ላይ በላዩ ሲመጣ የቀደመውን ግፍ ቶሎ ቶሎ እንረሳለን። አሁን ግን ቢያንስ በእነዚያ ታሪካዊ 540 ቀናት ውስጥ የተፈጸመውን አንረሳም ታሪካዊ ሰነድ አለ። ራሱ የግፍ ሰለባ የነበረው ጋዜጠኛው ሲሳይ አጌና ያንን ሰነድ ከጥሩ አተራረክና ለዛ ጋር ለናሙና አኑሮልናል። እንዲሁም ንዴትና ቁጭት ላነሰው፣ መነሳሳት ለጎደለው ሁሉ በቂ ሰነድ ነው። የሰው ልጅ ከዚህ በላይ ምን ሊደርስበት ይችላል? የኢትዮጵያ የፍትህ ሥርዓት በዚህ መንግሥት ዘመን ምን እንደነበረ ማጥናት ለሚፈልግ ሰው ጥሩ ማመሳከሪያ ነው። ወራት ቀናትና ሰዓታትን ይዞ፣ ዝርዝር አሃዝ አስደግፎ፣ የህግ አንቀጽ እያጣቀሰ የችሎት፣ የእስር ውሎና አዳሮችን ማካተቱ ሲታይ ብዙ ብዙ ተደክሞበታል። በመጽሐፉ ቅንጅቶችና ጋዜጠኞች ብቻ ሳይሆኑ ካህን፣ እብድ፣ አዛውንት፣ ወይዛዝርት ሳይቀሩ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች አሉበት። አሳዛኛና አስቂኝ ገጠመኞችም ሞልተውታል። ሲሳይ በዚያ ድካሙ ሊያሳየን የፈለገውን ነገር እንኳ ትተን፣ ራሳችን ማየት የምንችለውን ነገር ብቻ እንኳ ማየት ብንችል የዚያች አገር ሰቆቃ አጭር በሆነ ነበር። የቃሊቲው መንግሥት እንዲህ የሚያሰኝና ወደ ኋላ ተመልሶ ወደፊት ለማሰብ የሚያንደረድር መጽሐፍ ነው። ጥያቄም  ያጭራል፣ ሌሎች ላይ የደረሰው ግፍ የማያነሳሳን እንኳ ብንበዛ፣ ባንድም ሆነ በሌላ መንገድ በግፍ ታስሮና ተንገላቶ የወጣው ሰው ብዛት ግን በራሱ ለውጥ ለማምጣት የሚችል ህዝብ ይወጣዋል። በመጽሐፉ ውስጥ የሚርመሰመሰው የእስረኛ ብዛትና የግፉ ዓይነት ይህን ጥያቄ ያስነሳል።  

                                                                                                                                                      ጋዜጠኛ  ደረጀ ደስታ

     ሲሳይ አጌና የቃሊቲው መንግስት የማያወላውል ምስክርነቱን ሰጥቷል፤ለሰባት ያህል ጊዚያት ቢታሰርም፣በርካታ ማስፈራሪያና ዛቻ ከአቶ መለስ የአፈና ጋሻ ጃግሬዎች ቢገጥመውም፤በአቋሙ ጸንቶ አትጻፍ ሲባል እየከተበ፣አትናገር ሲባል እየተናገረ እነሆ በኢትዮጵያ እንዳይታተም የታገደውን መጽሓፍ በስደት ዘመኑ ለህትመት አብቅቷል።የቃሊቲው መንግስት ምርጫ ፱፯ን ተከትሎ በንጹህ ኢትዮጵያዊያን ላይ የተፈጸመውን አስገራሚና አሳዛኝ ታሪክ ይተርካል።ማን ያርዳ የቀበረ፣ማን ይናገር የነበረ እንዲሉ የቃሊቲው የግፍ ማእድ ተቋዳሽ የነበረው ጋዜጠኛ ሲሳይ አጌና የኢትዮጵያዊያንን ስቃይና ፍዳ በሰላ ብእሩ ከትቦልናል። የቃሊቲው መንግስት አስቸጋሪና ውስብስብ የሆነውን የምጥና የጣእር ግዜ ፍንትው አድርጎ ያሳየናል። በዚህ መጽሃፍ በአቶ መለስ ዜናዊ ተደርሶ በነሺመልስ ከማል የተተወነው የፍርድ ቤት ድራማ ገላልጦታል። ታሪክ ግን ግዜውን ጠብቆ መፍረዱ አይቀሬ ነው።

ጋዜጠኛ አበበ ገላው

 

Other Available Books
                











Netsanet Publishing Agency

 About Us
 Become an Affiliate
 Privacy Policy
 Send Us Feedback
 
Company Info | Advertising | Product Index | Category Index | Help | Terms of Use
Copyright © Netsanet Publishing Agency. All Rights Reserved.
Sell Online with Volusion.