
Main Line (800)672-6380State/city
|
Phone NO
|
State/city
|
Phone NO
|
|
Ottawa
|
613-400-1599
|
Dallas
|
214-727-7939
|
|
Calgary
|
403-478-8498
|
Houston
|
214-727-7939
|
|
Vancouver
|
604-318-0915
|
Denver
|
720-212-3592
|
|
Seattle
|
206-769-5446
|
DC
|
571-239-7001
|
|
Las
Vegas
|
702-719-9258
|
OH
|
614-989-1007
|
|
Boston
|
857-247-2002
|
MN
|
952-393-4700
|
“የቃሊቲው
መንግስት”
በሲሳይ
አጌና
ሲሳይ አጌና ነፃው ፕሬስ
ሲወለድ
የነበረ፣ እስከ ምርጫ 97ም
የቀጠለ ጋዜጠኛ ነው፤ታስሮ ፈቃድ እስኪከለከል ነጻው ፕሬስ ውስጥ
ኢትኦጵ ጋዜጣና መጽሄትን ሲያዘጋጅ ቆይቷል፤ነፃው
ፕሬስ ከፍተኛ እመርታ
ባሳየበት እና
ከፍተኛ አደጋ በደረሰበት
በምርጫ 97ም በከፍተኛ ደረጃ የተሳተፈና ከፍተኛውን ዱላ የተቀበለ
ጋዜጠኛ ነው፤
በአለፉት ሃያ አመታት ፕሬሱ ከአቶ መለስ መንግስት ጋር የሞት ሽረት ትግል ሲያደርግ ሲሳይ አጌና
ከግንባር ቀደሞቹ ውስጥ አንዱ ነው:: ለዚህም ውለታው የአቶ መለስን የተለያዩ እስርቤቶችን በተደጋጋሚ ጎብኝቷል፤
እንዲያውም የማዕከላዊ እስርቤት ቋሚ ደምበኛ ከሚባሉት ውስጥ ሲሳይ ቀዳሚ ነው፤ሲሳይ
በዚህ መፅሃፉ የቃሊቲውን እስር ቤትና የፍትህ ስርዓቱን ያስጎበኘናል:: አቀራረቡ እንደ ስርዓቱ ሰለባ ሆኖ ሳይሆን እንደ አንድ
ነፃ ጋዜጠኛ ዳር ሆኖ ፍርዱን ለአንባቢ በመተው ነው፤ ከብዕሩ በላይ ያስገረመኝ የበደል ስሜቱን ተቆጣጥሮ
ያልተዛባ ታሪክ ለትውልድ ለማስተላለፍ መጣሩ ነው፤
ይተኩሷል እንደ ገብርዬ ነበር ያለው ቴዎድሮስ?
ይታገሷል
እንደ ሲሳይ ልበል እኔም ::
አክቲቪስት እና አርቲስት
ታማኝ በየነ
አገርና
ወገን
ላይ
የሚሠራው
ግፍ
ላይ
በላዩ
ሲመጣ
የቀደመውን
ግፍ
ቶሎ
ቶሎ
እንረሳለን።
አሁን
ግን
ቢያንስ
በእነዚያ
ታሪካዊ 540
ቀናት
ውስጥ
የተፈጸመውን
አንረሳም
፤
ታሪካዊ
ሰነድ
አለ።
ራሱ
የግፍ
ሰለባ
የነበረው
ጋዜጠኛው
ሲሳይ
አጌና
ያንን
ሰነድ
ከጥሩ
አተራረክና
ለዛ
ጋር
ለናሙና
አኑሮልናል።
እንዲሁም
ንዴትና
ቁጭት
ላነሰው፣
መነሳሳት
ለጎደለው
ሁሉ
በቂ
ሰነድ
ነው።
የሰው
ልጅ
ከዚህ
በላይ
ምን
ሊደርስበት
ይችላል?
የኢትዮጵያ
የፍትህ
ሥርዓት
በዚህ
መንግሥት
ዘመን
ምን
እንደነበረ
ማጥናት
ለሚፈልግ
ሰው
ጥሩ
ማመሳከሪያ
ነው።
ወራት
ቀናትና
ሰዓታትን
ይዞ፣
ዝርዝር
አሃዝ
አስደግፎ፣
የህግ
አንቀጽ
እያጣቀሰ
የችሎት፣
የእስር
ውሎና
አዳሮችን
ማካተቱ
ሲታይ
ብዙ
ብዙ
ተደክሞበታል።
በመጽሐፉ
ቅንጅቶችና
ጋዜጠኞች
ብቻ
ሳይሆኑ
ካህን፣
እብድ፣
አዛውንት፣
ወይዛዝርት
ሳይቀሩ
የተለያዩ
የህብረተሰብ
ክፍሎች
አሉበት።
አሳዛኛና
አስቂኝ
ገጠመኞችም
ሞልተውታል።
ሲሳይ
በዚያ
ድካሙ
ሊያሳየን
የፈለገውን
ነገር
እንኳ
ትተን፣
ራሳችን
ማየት
የምንችለውን
ነገር
ብቻ
እንኳ
ማየት
ብንችል
የዚያች
አገር
ሰቆቃ
አጭር
በሆነ
ነበር።
“የቃሊቲው
መንግሥት”
እንዲህ
የሚያሰኝና
ወደ
ኋላ
ተመልሶ
ወደፊት
ለማሰብ
የሚያንደረድር
መጽሐፍ
ነው።
ጥያቄም ያጭራል፣
ሌሎች
ላይ
የደረሰው
ግፍ
የማያነሳሳን
እንኳ
ብንበዛ፣
ባንድም
ሆነ
በሌላ
መንገድ
በግፍ
ታስሮና
ተንገላቶ
የወጣው
ሰው
ብዛት
ግን
በራሱ
ለውጥ
ለማምጣት
የሚችል
ህዝብ
ይወጣዋል።
በመጽሐፉ
ውስጥ
የሚርመሰመሰው
የእስረኛ
ብዛትና
የግፉ
ዓይነት
ይህን
ጥያቄ
ያስነሳል።
ጋዜጠኛ
ደረጀ
ደስታ
ሲሳይ
አጌና
በ“የቃሊቲው
መንግስት”
የማያወላውል
ምስክርነቱን
ሰጥቷል፤ለሰባት
ያህል
ጊዚያት
ቢታሰርም፣በርካታ
ማስፈራሪያና
ዛቻ
ከአቶ
መለስ
የአፈና
ጋሻ
ጃግሬዎች
ቢገጥመውም፤በአቋሙ
ጸንቶ
አትጻፍ
ሲባል
እየከተበ፣አትናገር
ሲባል
እየተናገረ
እነሆ
በኢትዮጵያ
እንዳይታተም
የታገደውን
መጽሓፍ
በስደት
ዘመኑ
ለህትመት
አብቅቷል።“የቃሊቲው
መንግስት”
ምርጫ
፱፯ን
ተከትሎ
በንጹህ
ኢትዮጵያዊያን
ላይ
የተፈጸመውን
አስገራሚና
አሳዛኝ
ታሪክ
ይተርካል።ማን
ያርዳ
የቀበረ፣ማን
ይናገር
የነበረ
እንዲሉ
የቃሊቲው
የግፍ
ማእድ
ተቋዳሽ
የነበረው
ጋዜጠኛ
ሲሳይ
አጌና
የኢትዮጵያዊያንን
ስቃይና
ፍዳ
በሰላ
ብእሩ
ከትቦልናል።
የቃሊቲው
መንግስት
አስቸጋሪና
ውስብስብ
የሆነውን
የምጥና
የጣእር
ግዜ
ፍንትው
አድርጎ
ያሳየናል።
በዚህ
መጽሃፍ
በአቶ
መለስ
ዜናዊ
ተደርሶ
በነሺመልስ
ከማል
የተተወነው
የፍርድ
ቤት
ድራማ
ገላልጦታል።
ታሪክ
ግን
ግዜውን
ጠብቆ
መፍረዱ
አይቀሬ
ነው።
ጋዜጠኛ
አበበ
ገላው